በአዲስ አበባ ተቀማጭነታቸውን ያደረጉ የተለያዩ ሀገራት አምባሳደሮች እና የዲፕሎማቲክ ማህበረሰብ አባላት በልዩ ኢኮኖሚ ዞኖች ውስጥ ያሉ የልማት እንቅስቃሴዎችን፣ የኩባንያዎችን የሥራ ሂደት ተመልክተዋል።
በኢትዮጵያ የአሜሪካ ባለሙሉ ሥልጣን አምባሳደር ኤርቪን ማሲንጋ የሃዋሳ ልዩ የኢኮኖሚ ዞንን በመጎብኘት በዞኑ የሚከናወኑ የኢንዱስትሪና የኢንቨስትመንት እንቅስቃሴዎችን ተመልክተዋል።