በልዩ የኢኮኖሚ ዞኖች የአምራች ኢንዱስትሪ ተግዳሮቶችን ለመፍታት እና የኢንቨስትመንት ፍሰቱን ለማሳደግ የዘርፉ ባለድርሻ አካላት ተቀናጅተው መስራት እንዳለባቸው የጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ (ዶ/ር) የማክሮ ኢኮኖሚ ዘርፍ አማካሪ እና የብሄራዊ አምራች ኢንዱስትሪ ካውንስል ሰብሳቢ አምባሳደር ግርማ ብሩ ገለጹ፡፡
በጠቅላይ ሚኒስቴር አብይ አህመድ (ዶ/ር) የማክሮ ኢኮኖሚ አማካሪ አምባሳደር ግርማ ብሩ የተመራ የብሄራዊ የአምራች ኢንዱስትሪ ካውንስል አባላት በሐዋሳ ልዩ የኢኮኖሚ ዞን የመስክ ምልከታ አድርገዋል።
በኢትዮጵያ የጀርመን እና የእንግሊዝ ኤምባሲ ከፍተኛ የልኡካን ቡድን አባላት በሀዋሳ ልዩ የኢኮኖሚ ዞን በጀርመን ተራድኦ ድርጅት (GIZ) እየተከናወኑ ያሉ ፕሮጀክቶችን ጎብኝተዋል፡፡
የዓለም ባንክ የኢንዱስትሪ ፓርኮች ልማት ኮርፖሬሽን ወደ ቂሊንጦ ልዩ ኢኮኖሚ ዞን በመድሀኒት እና ህክምና ቁሳቁስ ምርት ዘርፍ ስመ-ጥር ባለሀብቶችን ለመሳብ የሚያደርገውን ጥረት እንደሚደግፍ አስታወቀ፡፡