የኮምቦልቻ ልዩ ኢኮኖሚ ዞን በጥራት ሥራ አመራር ስርዓት (ISO 9001:2015)፣ በአካባቢ ጥበቃ ሥራ አመራር ስርዓት (ISO 14001:2015) እና በሥራ ላይ ጤናና ደህንነት አስተዳደር ስርዓት (ISO 45001:2018) ከኢትዮጵያ ተስማሚነት ምዘና ድርጅት ዓለም አቀፍ እውቅና አግኝቷል።
የአዳማ ልዩ ኢኮኖሚ ዞን በጥራት ስራ አመራር ስርዓት (ISO 9001:2015) እና በአካባቢ ጥበቃ ስራ አመራር ስርዓት (ISO 14001:2015) ከኢትዮጵያ ተስማሚነት ምዘና ድርጅት ዓለም አቀፍ እውቅና አግኝቷል።
የኢንዱስትሪ ልማትን ከኤሌክትሪክ ልማት ለይቶ ማሰብ መኪናን ያለ ሞተር እንደ ማሰብ መሆኑን የኢንዱስትሪ ፓርኮች ልማት ኮርፖሬሽን ዋና ሥራ አስፈጻሚ ዶ/ር ፍሰሃ ይታገሱ ገለጹ።
የኢንዱስትሪ ፓርኮች ልማት ኮርፖሬሽን ለሆቴልና አፓርትመንት አገልግሎት የሚውል አንድ ባለአምስት ወለል ሕንፃን ጨምሮ የተለያዩ ፕሮጀክቶችን በሀዋሳ ልዩ ኢኮኖሚ ዞን አስመረቀ።