የኢንዱስትሪ ፓርኮች ልማት ኮርፖሬሽን በሚያስተዳድራቸው ልዩ የኢኮኖሚ ዞኖች ውስጥ አቅም ያላቸው የቻይና ባለሀብቶች ለመሳብ በኢትዮጵያ የቻይና ኤምባሲ ድጋፍ እንዲያደርግ የኢንዱስትሪ ፓርኮች ልማት ኮርፖሬሽን ዋና ስራ አስፈጻሚ ዶ/ር ፍሰሃ ይታገሱ ጠየቁ፡፡
ግብርና መር የሆነውን የሃገራችን ኢኮኖሚ ወደ ኢንዱስትሪ ለማሸጋገር በሚደረገው ጥረት ውስጥ በመላው ሃገሪቱ በሚያስተዳድራቸው 14 የኢንቨስትመንት ማእከላቱ ውስጥ የሃገር ውስጥ ባለሃብቶች ንቁ ተሳታፊ እንዲሆኑ በትኩረት በመስራት ላይ መሆኑን የኢንዱስትሪ ፓርኮች ልማት ኮርፖሬሸን ምክትል ስራ አስፈፃሚ አቶ ፍፁም ከተማ ገለፁ።
የአውሮፓ ህብረት–ኢትዮጵያ የቢዝነስ ፎረም ተሳታፊ የነበሩ የቢዝነስ ልዑካን ቡድን አባላት የቦሌ ለሚ እና ቂሊንጦ ልዩ የኢኮኖሚ ዞኖችን ጎብኝተዋል።
የኢንዱስትሪ ፓርኮች ልማት ኮርፖሬሽን በስሩ የሚያስተዳድራቸው ተቋማት ዓለም አቀፍ ተወዳዳሪነታቸውን ለማሳደግ የሚረዱ ዓለም አቀፍር አሰራሮች ተግባራዊ እንዲደረጉ የሚደረገው ጥረት ተጠናክሮ እንደሚቀጥል የኮርፖሬሽኑ ፓርክ ኦፕሬሽን እና አስተዳደር ዘርፍ ስራ አስፈጻሚ አቶ ፍጹም ከተማ ገለጹ፡፡