በፓኪስታን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ከፍተኛ ዲፕሎማት አምባሳደር ሀሚድ አስጋር ካህን የተመራ የቢዝነስ ልዑካን ቡድን አባላት የቂሊንጦ ልዩ የኢኮኖሚ ዞንን ጎብኝቷል፡፡
የኢንዱስትሪ ፓርኮች ልማት ኮርፖሬሽን በሚያስተዳድራቸው ልዩ የኢኮኖሚ ዞኖች ያለውን የቻይናውያን ባለሃብቶች ተሳትፎ ለማሳደግ በትኩረት እንደሚሰሩ የቻይና ብሔራዊ የንግድ ምክር ቤት ምክትል ፕሬዚዳንት ዣንግ ሚን ገለጹ፡፡
የኢንዱስትሪ ፓርኮች ልማት ኮርፖሬሽን ዋና መስሪያ ቤትና በአዲስ አበባ የሚገኙ ቅርንጫፎች የስራ መሪዎችና ሰራተኞች 22ኛውን ዓለም አቀፍ የጸረ ሙስና ቀንን“ትውልድን በሥነ-ምግባር፤ ተቋምን በአሠራር” በሚል መሪ ቃል በተለያዩ ዝግጅቶች ትናንት አክብረዋል።
በኢትዮጵያ ዉስጥ የመንግስት የልማት ድርጅቶች ተብለዉ የሚታወቁ ወደ አርባ (40) ድርጅቶች ሲኖሩ ከለዉጡ መንግስት የፖለቲካና ኢኮኖሚ ሪፎርም በፊት በመንግስት ልማት ድርጅቶች ይዞታና አስተዳደር(Public Enterprises Holding Agency/PEHA) ክትትልና ቁጥጥር ስር ሆነዉ አስተዳዳሪ ቦርድ እየተሾመላቸዉ ባለቤትነታቸዉም የኢ.ፌ.ዲ.ሪ መንግስት( የገንዘብ ሚኒስቴር) ሆኖ በኢኮኖሚዉ ዉስጥ ሲንቀሳቀሱ ቆይተዋል፡፡