የኮርፖሬሽኑ የ10 ዓመታት ጉዞ ለድሬዳዋ ከተማ እድገት የራሱን አሻራ ማኖር ችሏል፡-ከድር ጁሃር
የኢንዱስትሪ ፓርኮች ልማት ኮርፖሬሽን በሚቀጥሉት 10 አመታት ልዩ ኢኮኖሚ ዞኖችን በሀገር ውስጥ ከማስፋፋት በተጨማሪ በተለያዩ የአፍሪካ ሀገራት ዞኖቹን በማልማት ለአህጉራዊ ኢኮኖሚያዊ ትስስር የበኩሉን አዎንታዊ ሚና የሚጫወት ግዙፍ የመንግስት የልማት ድርጅት እንደሚሆን የኮርፖሬሽኑ ዋና ስራ አስፈጻሚ ዶ/ር ፍሰሃ ይታገሱ ገለጹ፡፡
በመላው ሀገሪቱ የተገነቡት ልዩ የኢኮኖሚ ዞኖችና ነፃ የንግድ ቀጠና በሚገኙበት አካባቢ ለሚገኙ ከተሞች የኢኮኖሚ እድገትና ለሀገር ኢንዱስትሪ መስፋፋት ያበረከቱት አስተዋጽኦ ከፍተኛ መሆኑን የኢንዱስትሪ ፓርኮች ልማት ኮርፖሬሽን ዋና ስራ አስፈፃሚ ፍሰሃ ይታገሱ (ዶ/ር) ገለፁ።