• Striving for eco industrial park
logo

የቻይና የባለሃብቶች ልዑካን ቡድን የቂሊንጦ ልዩ የኢኮኖሚ ዞንን ጎበኘ

የቻይና የባለሃብቶች ልዑካን ቡድን የቂሊንጦ ልዩ የኢኮኖሚ ዞንን ጎበኘ

ሀያ ስድስት አባላትን ያቀፈ የቻይና ባለሃብቶች የልዑካን ቡድን የቂሊንጦ ልዩ የኢኮኖሚ ዞንን የስራ እንቅስቃሴ ተዘዋውረው ጎብኝተዋል፡፡

የልዑካን ቡድኑ አባላትን ተቀብለው ያነጋገሩት የዋና ስራ አስፈጻሚ ጽ/ቤት ሃላፊ ተወካይ አቶ ታሪኩ አዱኛ የኢንዱስትሪ ፓርኮች ልማት ኮርፖሬሽን በሚያስተዳድራቸው ልዩ የኢኮኖሚ ዞኖች እና ኢንዱስትሪ ፓርኮች ያሉ የመሰረተ ልማት አቅርቦቶችና ለባለሃብቶች በሚሰጡ የተለያዩ ማበረታቻዎች ዙሪያ ገለጻ አድርገውላቸዋል፡፡

የልዑካን ቡድኑ አባላት በበኩላቸው በፋርማሲዩቲካል የኢንቨስትመንት ዘርፍ ለባለሃብቶች በሚሰጡ ማበረታቻዎችና በመንግስት በኩል የሚደረገውን ድጋፍ አስመልክቶ ጥያቄ ያቀረቡ ሲሆን በቀጣይም ገብተው ኢንቨስት ለማድረግ የሚሰሩ መሆኑን ገልጸዋል፡፡

የፋርማሲዩቲካል የኢንቨስትመንት ዘርፍን ለማበረታታት በመንግስት በኩል የሚደረጉ ድጋፎችንና በኮርፖሬሽኑ በኩል እየተሰሩ ያሉ ስራዎችን አስመልክቶ ማብራሪያ በቂሊንጦ ልዩ የኢኮኖሚ ዞን ምክትል ስራ አስኪያጅ አቶ ምስክር ማሞ ማብራሪያ ተሰጥቷቸዋል፡፡  

የኢንዱስትሪ ፓርኮች ልማት ኮርፖሬሽን በሚያስተዳድራቸው 11 ልዩ የኢኮኖሚ ዞኖች እና 3 ኢንዱስትሪ ፓርኮች ውስጥ ገብተው በመስራት ላይ ካሉ የውጪ ባለሃብቶች ውስጥ ቻይናውያን ባለሃብቶች ከፍተኛውን ድርሻ ይይዛሉ፡፡

#IPDC 
#EcoGreenSEZs  
#GreenIndustrialization 
#CircularEconomy 
#GreenLegacyInitiative
#EVTransport 
#SustainableManufavcturing 
#ClimateResilience 
#LowCarbonDevelopment 
#Ethiopia
#exportprocessingzone 
#SpecialEconomicZones
#madeinethiopia
#madein
#InvestInEthiopia
#InvestEthiopia 
#HawassaSEZ 
#TextileHub 
#PlugAndPlay 
#AfricaRising 
#manufactureinafrica
#pharmaceuticals

በዌብሳይት - https://ipdc.gov.et/ 
በፌስቡክ - https://www.facebook.com/IPDCEthiopiaofficial 
በትዊተር (ኤክስ) - https://x.com/EthiopiaIpdc 
በቴሌግራም - https://t.me/ipdcofficial 
በሊንክድ ኢን - https://www.linkedin.com/company/ipdcethiopiaofficial 
በኢንስታግራም - https://www.instagram.com/ipdc_et 
በዩቲዩብ - https://www.youtube.com/@IPDCETHIOPIA 
በቲክቶክ - https://www.tiktok.com/@ipdc_ethiopia 
በቴሌግራም ቦት፡- https://t.me/ipdctchatbot
በዋትስአፕ፡- https://whatsapp.com/channel/0029VakCUHKJP21D0s3OEB30