• +251118722266
  • Striving for eco industrial park
logo
  • by admin
  • 0Comments
  • 11 months, 3 weeks ago
  • 355 Views

የኮርፖሬሽኑ ማህበራዊ ኃላፊነት

የኢንዱስትሪ ፓርኮች ልማት ኮርፖሬሽን በአዳማ ከተማ በ100 ሚሊዮን ብር ለሚያስገነባው ትምህርት ቤት የመሰረት ድንጋይ ተቀመጠ 

የኢንዱስትሪ ፓርኮች ልማት ኮርፖሬሽን ከአዳማ ከተማ አስተዳደር ጋር በመተባበር በአዳማ ከተማ ቡኩ ሸነን ቀበሌ በ100 ሚሊዮን ብር ወጪ ለሚያስገነባው ትምህርት ቤት የመሰረት ድንጋይ በዛሬው እለት ተቀምጧል። 

የመሰረት ድንጋዩን የኮርፖሬሽኑ ዋና ስራ አስፈፃሚ አክሊሉ ታደሰ እና የአዳማ ከተማ ከንቲባ ሀይሉ ጀልዴ እንዲሁም የከተማው ከፍተኛ አመራሮች ከአባገዳዎች እና ከሀደ ሲንቄዎች ጋር በጋራ አስቀምጠዋል። 

ኮርፖሬሽኑ በአዳማ ኢንዱስትሪ ፓርክ አማካኝነት የሚያስገነባው ትምህርት ቤቱ በተለያዩ የግንባታ ምዕራፎች ከቅድመ መደበኛ እስከ መሰናዶ የትምህርት ደረጃ የሚገነባ ሲሆን የስፖርት ሜዳ፤ የተማሪዎች ማረፊያና መዝናኛ፤ የአትክልትና አረንጓዴ ስፍራን በማካተት ለትምህርት ቤቱ አስፈላጊ የሚሆኑ የትምህርት መገልገያ መሳሪያዎች የሚሟሉለት መሆኑ ታውቋል። 

የኢንዱስትሪ ፓርኮች ልማት ኮርፖሬሽን ዋና ስራ አስፈፃሚ አክሊሉ ታደሰ ግንባታው በታቀደለት ጊዜ በጥራት እንዲከናወን እንዲሁም የመጀመሪያው ምዕራፍ በአንድ ዓመት ውስጥ ተጠናቆ ለአገልግሎት ዝግጁ እንዲሆን ኮርፖሬሽኑ አስፈላጊውን የድጋፍና ክትትል ስራ ያለማቋረጥ እንደሚያከናውን አሳውቀዋል።