• +251118722266
  • Striving for eco industrial park
logo
  • by admin
  • 0Comments
  • 1 year, 2 months ago
  • 427 Views

የፖርቹጋል ባለሀብቶች በኢንዱስትሪ ፓርኮች

የፖርቹጋል ባለሀብቶች በኢንዱስትሪ ፓርኮችና በድሬዳዋ ነፃ ንግድ ቀጠና ምዋዕለ ንዋያቸውን እንዲያፈሱ ተጠየቀ

የፖርቹጋል ባለሀብቶች በኢንዱስትሪ ፓርኮችና በድሬዳዋ ነፃ ንግድ ቀጠና በዘርፈ ብዙ የኢንቨስትመንት አማራጮች እንዲሰማሩ የኢንዱስትሪ ፓርኮች ልማት ኮርፖሬሽን ዋና ስራ አስፈፃሚ አክሊሉ ታደሰ ጥሪ አቅርበዋል

ዋና ስራ አስፈፃሚው ጥሪውን ያቀረቡት ከልዑካቸው ጋር በኢትዮጵያ የፖርቹጋል አምባዳሰር ከሆኑት ሉዊዛ ፍራጎሶ ጋር በተወያዩበት ወቅት ነው።

በውይይታቸውም ኢትዮጵያና ፖርቹጋል በኢንቨስትመንት፣ በኢኮኖሚ እና በሌሎች የትብብር መስኮች ያላቸውን ግንኙነት አጠናክረው መቀጠል በሚችሉባቸው ጉዳዮች ላይ ሀሳብ ተለዋውጠዋል።

በቀጣይም ሁለቱ አገራት በተለይም የኢንቨስትመንት ግንኙተታቸው ተጠናክሮ እንዲቀጥልና የፖርቹጋል ባለሀብቶች ወደ ኢትዮጵያ በመምጣት ኮርፖሬሽኑ በሚያስተዳድራቸው ኢንዱስትሪ ፓርኮችና ድሬዳዋ ነፃ ንግድ ቀጠና በዘርፈ ብዙ ኢንቨስትመንቶች እንዲሰማሩ ለማድረግ ስራዎች እንዲሰሩ ከመግባባት ተደርሷል።