በናሚቢያ ሪፐብሊክ የከተማና ገጠር ልማት ሚኒስትር ጄምስ ሳንክዋሳ የተመራው ከፍተኛ የመንግሥት ልዑካን ቡድን አባላት የኢትዮጵያን የኢንዱስትሪ ልማት ልምድ ለመገንዘብ የቦሌ ለሚ እና ቂሊንጦ ልዩ የኢኮኖሚ ዞኖችን ጎበኙ።
የኢንዱስትሪ ፓርኮች ልማት ኮርፖሬሽን ከCO3 ኢነርጂ ኩባንያ ጋር ከልዩ የኢኮኖሚ ዞኖች የሚወጡ ተረፈ ምርቶችን ወደ አማራጭ የኃይል ምንጭ በመቀየር ወደ ገበያ ለማቅረብ የሚያስችል የመግባቢያ ስምምነት ተፈራርመዋል።
በተለያዩ የኢንቨስትመንት ዘርፎች ከ8 በላይ ሀገራት የተሰማራው የአፍሪካ ኢንቨስትመንት ግሩፕ ልዑካን ቡድን አባላት ግሩፑ ሀብቱንና የኢንዱስትሪ ልማት እውቀቱን በኢንዱስትሪ ፓርኮች ልማት ኮርፖሬሽን በሚተዳደሩ ልዩ የኢኮኖሚ ዞኖች ላይ ለማዋል ስለሚችልበት አግባብ ከኮርፖሬሽኑ አመራሮች ጋር ተወያይቷል።
የኢንዱስትሪ ፓርኮች ልማት ኮርፖሬሽን ከኢትዮጵያ ኢንተርፕረነርሺፕ ልማት ኢንስቲትዩት ጋር በተለያዩ የልማት መስኮች በጋራ ለመስራት የሚያስችል የመግባቢያ ስምምነት (MoU) ተፈራርሟል።